Friday, May 18, 2012
BREAKING NEWS በአሜሪካ ስብሰባ ላይ የሚገኙት አቶ መለስ ዜናዊ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ ገና መናገር ሲጀመሩ በጋዜጠኛ አበበ ገላው ከፍ ባለ ድምፅ ተቃውሞ ገጠማቸው
በአሜሪካ ስብሰባ ላይ የሚገኙት አቶ መለስ ዜናዊ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ ገና መናገር ሲጀመሩ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ከፍ ባለ ድምፅ፤ “ይህ ሰው ነብሰ ገዳይ ነው… ወንጀለኛ ነው… እዚህ ቦታ ሊገኝ አይገባውም” ሲል በተሰብሳቢዎች ፊት ተቃውሞውን አሰማ ሲል ኢሳት ዘገበ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዳራሽ ውስጥ እንዲህ ያለ የተቃውሞ ያጋጥመኛል ብለው ስላላጠበቁ ተደናግጠው ንግግራቸውን አቆርጠው እንደነበር ኢሳት በዘገባው ገልጿል።አበበን የፀጥታ ሀይሎች በሰላም ከአዳርሽ እንዲወጣ እንዳደረጉት ኢሳት ገልጿል።
አቶ መለስ በአለም አቀፍ መድረክ ላይ ንግግር
ለማድረግ ሲሄዱ ተቃውሞ ሲገጥማቸው የመጀመርያው ባይሆንም የጋዜጠኛ አበበ ገላው ጠቃውሞ ግን አቶ መለስን ያስደነገጠ እና በአቶ
መለስ ላይ ተቃውሞው መጠንከሩን ለአለም ህብረተሰብ ያሳየ ነው ሲሉ ታዛቢዎች ይናገራሉ።
Subscribe to:
Posts (Atom)