Friday, May 18, 2012

ጋዜጠኛ አበበ ገላው ከፍ ባለ ድምፅ ያሰማውን ተቃውሞ በቪዲዮ ይመልከቱ ::Ethiopian Journalist Abebe Gellaw Confronted Meles Zenawi (Video)


BREAKING NEWS በአሜሪካ ስብሰባ ላይ የሚገኙት አቶ መለስ ዜናዊ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ ገና መናገር ሲጀመሩ በጋዜጠኛ አበበ ገላው ከፍ ባለ ድምፅ ተቃውሞ ገጠማቸው



በአሜሪካ ስብሰባ ላይ የሚገኙት አቶ መለስ ዜናዊ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ ገና መናገር ሲጀመሩ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ከፍ ባለ ድምፅ፤  “ይህ ሰው ነብሰ ገዳይ ነውወንጀለኛ ነውእዚህ ቦታ ሊገኝ አይገባውምሲል በተሰብሳቢዎች ፊት ተቃውሞውን አሰማ ሲል ኢሳት ዘገበ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዳራሽ ውስጥ እንዲህ ያለ የተቃውሞ  ያጋጥመኛል ብለው ስላላጠበቁ ተደናግጠው ንግግራቸውን አቆርጠው እንደነበር  ኢሳት በዘገባው ገልጿል።አበበን የፀጥታ ሀይሎች በሰላም ከአዳርሽ እንዲወጣ እንዳደረጉት ኢሳት ገልጿል።
አቶ መለስ በአለም አቀፍ መድረክ ላይ ንግግር ለማድረግ ሲሄዱ ተቃውሞ ሲገጥማቸው የመጀመርያው ባይሆንም የጋዜጠኛ አበበ ገላው ጠቃውሞ ግን አቶ መለስን ያስደነገጠ እና በአቶ መለስ ላይ ተቃውሞው መጠንከሩን ለአለም ህብረተሰብ ያሳየ ነው ሲሉ ታዛቢዎች ይናገራሉ።

Friday, May 11, 2012

Eskinder, Andualem's trial POSTPONED



Addis Neger
The long anticipated verdict on Andualem Arage, Eskinder Nega and others 22 defendants POSTPONED to July 21 (Sene 14).

The session that lasted only for 10 minutes attracted many journalists and observers including the USA and UK ambassadors. The judges announced that, in the most grumbling explanation common to all political trials, they cannot give the verdict because “they couldn’t get the file copied [or transcribed] in time” (filu betsihuf tegelbito selaldereselen). The court hasn’t specified what kind of files are to be copied or transcribed that needed a month and half till the next session. Neither is known if the judges actually gave a decision or waiting for a direction from the political establishment.

The main reason to postpone the trial could be the ongoing World Economic Forum meeting and the media attention came with it.

Andualem and Eskinder were in good spirit and shape as a journalist attended the session told Addis Neger.

Breaking News : Students Protest in Bahir Dar and Gonder Universities


By Derese Tariku, for De Birhan 
Addis Abeba
09 May 2012

Following the protests and arrest of students of Debre Markos University, northern Ethiopia, in the past two days, the students of Bahir Dar University and Gonder University have began large scale protests today. It has been confirmed that both Poly and Peda Campuses of Bahir Dar University (BDU) and Tewodors and Maraki Campuses of Gonder University (GU) have spent the whole day today (09May 2012) protesting. "The student's protest is spreading like a wildfire" said a student from Maraki Campus, GU.  Regional police force and Federal police are approaching the campuses.
Several students have been injured and arrested following "rights related" protests by Debre Markos University  students in the past two days. "Food poison" is also said to be one of the causes.
There are over 40,000 students in both Bahir Dar and Gonder Universities enrolled in the regular program.

Saturday, May 5, 2012

በአቶ መለስ መንግስትና በኢትዮጵያ ሙስሊሞች መካከል የተፈጠረው ውጥረት አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል



ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ /  
የብዙሀኑ ሙስሊም አስተባባሪ ኮሚቴ፤በሀሰት ፕሮፓገጋንዳ የመብት ጥያቄዎቻችን አይዳፈኑም”  በሚል ርዕስ ባለ 15 ገጽ መግለጫ በበተነበት በትናንትናው ዕለት፤ መንግስት  በተቃራኒው የማስጠንቀቂያ እና የማስፈራሪያ መግለጫ አወጣ ሲል ኢሳት ዘገበ።
 የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴርን ዋቢ ያደረገው ይህው የኢሳት ዘገ ባ መንግስት ያወጣውን መግለጫ፤ በሙስሊም  ህብረተሰብ  ዘንድ እየተነሳ ያለውን ጥያቄና ተቃውሞ፤ በምርጫ 97 ወቅት ተከስቶ ከነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር አመሳስሎታል ብሏል።
 “መንግስት  ለእስልምና እምነትና ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ካለው አክብሮት በመነሳት  እያሳዬ ያለው ሰፊ ትዕግስት፤ የተቃውሞው አስተባባሪ የሆነው  ህገ ወጥ ሀይል  ከፍርሀት እየተመለከተው  ነውሲልም- የአቶ መለስ መንግስት አለመፍራቱን ጠቅሷል።
 እንደ መንግስት መግለጫ፤ ላለፉት 11 ሳምንታት አወሊያ እና በአንዋር መስጊድ  እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ   የብዙሀኑ ሙስሊም ጥያቄ ሳይሆን፤ህግና ስርዓትን አክብረው ለመሄድ ዝግጁነት በሌላቸው ሀይሎች  የሚመራ ነው።
 “ እነዚህ ወገኖች  መንግስትም ሆነ የህዝበ ሙስሊሙ ተቋም የየራሳቸውን ምላሽ እንዳልሰጧቸው በማስመሰል ሰፊ አፍራሽ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እያካሄዱ ከመሆኑም በላይ፤ 1997 ሀገሪቱን ለብጥበጥ ዳርገው ከፍ ያለ ጉዳት ካደረሱትና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ከተመደቡ ሀይሎች የጥፋት እንቅስቃሴ ጋር በግላጭ ተመጋጋቢ የሆነ ዘመቻም እያካሄዱ ነውሲልምየሀይማኖታችን ይከበር!’ ጥያቄ ባነሱ ሙስሊሞች ላይ ፖለቲካዊ ክስ አሰምቷል።
መግለጫው አያይዞም፦መንግስት ያሳየውን ትእግስት ከድክመት በመቁጠር መንግስት ፀረ ህገ መንግሰት ሆኗል-ስለዚህ በህገ መንግስቱ የተጎናፀፍናቸውን መብቶች ሊነጥቀን ተነስቷል በማለት እየተቀሰቀሰ ነውብሏል።
 እነዚህ ወገኖች ፖል ቶክና ፌስቡክን የመሳሰሉ ዘመናዊ ሚዲያዎችን ለፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ በማዋል ግርግርና ሁከት እንዲስፋፋ ከሚሹ በሀገር ውስጥ በሚነገሩ ቋንቋዎች ከሚተላለፉ የውጭ ሚዲያዎች ጋር በመቀናጀት በሀገሪቱ መንግስት ላይ የሚያካሂዱት የማጥላላት ዘመቻ መረን የለለቀበበት ደረጃ ደርሷል ሲልም- የፌዴራል ጉዳዮች መግለጫ አብራርቷል።
 በኢትዮጵያ ህገ መንግስት መሰረት መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ እንደማይገባ የተደነገገ ቢሆንም፤ አቶ መለስና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት በሀይማኖት ውስጥ ጣልቃ በመግባት ኢትዮጵያ ሙስሊሞች የአህባሽን አስተምህሮ እንዲከተሉ፤ እንዲሁም ባልመረጧቸውና አይወክሉንም ባሏቸው የመጂሊስ አመራሮች እንዲመሩ ግፊት በማድረግ ላይ መሆናቸው ይታወቃል።
 የተቃውሞው መንስኤም ሆነ እስካሁን ድረስ ህዝበ-ሙስሊሙ በሚያደርጋቸው ተቃውሞዎች እያቀረባቸው ያሉት ጥያቄዎችም በዋነኝነት ከነዚሁ ሁለት ነጥቦች ጋር የተያያዘ ነው- ያልመረጥነው የመጂሊስ አመራር ይነሳልን! መንግስት የአህባሽን አስተምህሮ በግዳጅ ህዝበ-ሙስሊሙ ላይ ለመጫን ከሚያደርገው እንቅስቃሴ ያቁም!” የሚሉ።
 የህዝበ-ሙስሊሙ ጥያቄዎች  በሀይማኖታዊ መብት መከበር ዙሪያ ላይ ያነጣጠሩ ከመሆናቸውም በላይ እስከዛሬ ድረስ በመስጂዳቸው ተወስነው ባሰሙት ተቃውሞ  በተደጋጋሚ፦መንግስት ድምፃችንን ይስማ!” እያሉ ሲጠይቁ መደመጣቸው ይታወቃል።
 የአቶ መለስ መንግስት ፤አንድ ጊዜ ከአክራሪዎችና ከአሸባሪዎች፤ ሌላ ጊዜ ከተቃዋሚ ሀይሎችናኪራይ ሰብሳቢዎችከሚላቸው ወገኖች ጋር እያገናኘ ፖለቲካዊ ምስል እየሰጠው ያለው ፤ይህንየሀይማኖታዊ መብት ይከበር!” ጥያቄ ነው።
ከዚህም አልፎ በአርሲ-አሰሳ ከተማ በመስጊዳቸው ተወስነው የተቃውሞ ድምጽ ሲያሰሙ በነበሩ ሙስሊሞች ላይ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ተኩስ ከፍተው ሰባት መግደላቸው እና በርካቶችን ማቁሰላቸው ይታወሳል።
 ግድያውን ተከትሎ  ትናንት የፌዴራል ጉዳዮች ያወጣው መግለጫ፤መንግስት መጠነ ሰፊ የሀይል እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱን የሚያመለክት ነው።
 የብዙሀኑ ሙስሊም አስተባባሪ ኮሚቴ ደግሞ፦በሀሰት ክስና ፕሮፓጋንዳ የሙስሊሙን ጥያቄ አዳፍናለሁ ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ  መሆኑን ነው ያሰመረበት።
 “ እውነትን እስከያዝን ድረስ፤በሀሰት ተወንጅለን እንታሰራለን ብለን አንፈራም! እንሞታታለን እንጂ ከመብት ጥያቄያችን ወደ ሁዋላ አናፈገፍግምነው  እያሉ  ያሉት ብዙሀኑ ሙስሊሞች።
 ለዚህም ይመስላል አሰሳ ሰባት ሙስሊሞች  በተገደሉና ሳምንት እና መንግስት  የማስጠንቀቂያ መግለጫ ባወጣ ማግስት  በዋለው በዛሬው የጁምአ ጸሎት እንደ ወትሮው ሁሉ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሙስሊሞች  ጠንካራ የተቃውሞ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ውለዋል።
 ለመንግስት መግለጫ ቀጥተኛ ምላሽ በሚመስል መልኩ መቶሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በአንዋር መስኪድ ተገኝተው በአርሲ አሳሳ ከተማ የተገደሉት ሰዎች አሸባሪዎች አለመሆናቸውን እና የመጅሊስ አመራሮችም ከስልጣን ወርደው ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። ድርጊቱን በስፍራው ተገኝቶ በፊልም የቀረጸው የኢሳት ዘጋቢ እንዳለው በዛሬው እለት የነበረው ተቃውሞ ሙስሊሙ ማህበረሰብ መንግስት ላወጣው መግለጫ ቁብ እንዳልሰጠው የሚያመለክት ነው።
 ይህ በእንዲህ እንዳለ በጎፋ አካባቢ በሚገኘው ጀሙ መስጊድ ሌሊቱን ከፍተኛ የሆነ ተኩስ እንደነበር፣ በአካባቢው የሚገኙ የሙስሊም መሪዎችን ለመያዝ ጥረት መደረጉን ለማወቅ ተችሎአል። በሼክ ኮጀሌ መስጊድ ደግሞ 10 ሰዎች ተይዘው ታስረዋል። አዎልያ ኮሌጅም ዛሬ ተዘግቶ መዋሉን መረጃዎች ደርሰውናል። መረጃዎቹን ከመንግስት በኩል ለማጣራት ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።