Friday, April 27, 2012

ሰርካለም ፋሲል የባለቤቷን የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሽልማት ልትቀበል ነው


አዲስ ቪው ሚዲያ
ኤፕሪል 27 2012
የ2012 PEN/Barbara Goldsmith Freedom to Write Award አሸናፊ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሽልማት ላይ ባለቤቱ ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እንደምትገኝ የአዲስ ቪው ምንጮች ገለጹ።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ተከሶ ጉዳዩን በፍርድ ቤት እየተከታተለ ባለበት ወቅት “ፔን ፍሪደም አዋርድ” የተባለውን አለም አቀፍ ሽልማትን አግኝቷ።ፔን አሜሪካን ሴንተር  የተባለው አለማቀፍ ድርጅት ጋዜጠኛ እስክንድር ለሰራቸው ስራዎች እውቅና በመስጠት ለ26ኛውን ሽልማት  ለጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል

ፔን አሜሪካን ሴንተር  ባዘጋጀው እና ሜይ 1 2012 በኒውዮርክ ሲቲ American Museum of Natural History በሚካሄደው የሽልማት ፕሮግራም ላይ የጋዜጠኛ እስክንድር ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካልም ተጋባዥ ሆና እንደምትገኝ እና ሽልማቱንም ትቀበላለች ተብሎ ይጠበቃል።

ከሰርካለም በተጨማሪ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ የሆኑ ድርጅት ሀላፊዎች እንዲሁም የቀድሞ አንድነት ሊቀመንበር የነበሩት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የዝግጅቱ ታዳሚዎች እንደሚሆኑ ታውቋል። ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በ2007 Courage in Journalism Award የተሰኘውን ሸልማት ከ  IWMF (International Women's Media Foundation) ማግኘቷ እና ከሽልማቱ ያገኘችውን ገንዘብ ለአምንስቲ ኢንተርናሽናል መለገሷ ይታወሳል።     

Thursday, April 26, 2012

ህዝባዊ ዓመፀን በዲጅታል ዘመን ጥቅም ላይ ማዋል


ደ ብርሃን ሚድያ
26 April ፳፩፪ 

ገነ ሻርፕ (Gene Sharp ) ሃይል ያልተቀላቀለበትን ህዝባዊ አመፀ/ ንቅናቄ  ካጠኑት      ሰዎች ግንባር ቀደሙ ነው። አንድአንድ  ሰዎች የሻርፕ መፀሃፍት በአለፉት ሃያ አመታት ወስጥ በነበሩት ለውጦች ወስጥ ሰፊ ሚና ነበራቸው ይላሉ፣ ከሚሎሶቪች አስከ ሙባረክ ውድቀት ድረስ።  "ሃይል ያልተቀላቀለበት ንቅናቄ ዘዴዎች" በሚለው ማኗሉ  ሻርፕ መቶ ዘጠናስምንት ዘዴዎችን ይዘረዝራል (list of 198 methods )። እነዚህ አምባገነን መንግስቶቺን መጣያ ዘዴዎች ደግሞ በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላሉ :- ሃይል ያልተቀላቀለበት ተቃውሞ አና ግፊት ማሳደር፣ አለመተባበርና ሃይል  ያልተቀላቀለበት ጣልቃ ገብነት ናቸው። እነዚሕ  ዘዴዎች ዛሬም ድረስ ጠቃሚ ቢሆኑም በዘመነ  ዲጅታል/ ኮምፒዩተር  አነዚሕኑ ዘዴዎች ከወቅቱ ጋር ማስኬድ ብሎም አዳዲስ  ዘዴዎቺን መፍጠሩ ጠቃሚ ነው ።

የሻርፕን መቶ  ዘጠናስምንት ዘዴዎች  መሰረት በማድረግ ታዋቂው የአይ ሪቭኦውሊሽን ድሕረ ገጸ   አዘጋጅ ዶክተር ፓትሪክ ሜር  አና ባልደረባው አንዴት አነዚሕን ዘዴዎች በዘመነ  ዲጅታል/ኮምፒዩተር  አንዴት ማሳደግ አንደሚቻል የሚጠቁም ዶከመንት አዘጋጀተዋል። አርሶም አነዚሕኑ ዘዴዎች ያንብቡ፣ ለወዳጆቸዎት ሁሉ ያስነበቡ አንዲሁም አርሶም አነዚሕን ዘዴዎች አንዴት ማሳደግ አንደሚቻል ያሎትን ሃሳብ ሳይን አፕ በማረግ ያኑሩ። 
ወደ ዳታቤዙ ወስጥ ለመግባት ይሄን    ጠቅ ያርጉ ። 

http://www.debirhan.com/2012/04/blog-post.html

Tuesday, April 24, 2012

በአዲስ አበባ አንድ ወጣት እራሱን ማቃጠሉ ተሰማ


ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-አንድ ጎልማሳ ኢትዮጵያዊ ዛሬ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ በመሐል አዲስ አበባ ጊዮርጊስ ዳግማዊ ምኒልክ ሃውልት ፊት- ለፊት በሚገኘው የአውቶብስ መቆሚያ ጎዳና ፤ አዲስ ምሩቅ ተማሪዎች የሥራ ማስታወቂያ የሚመለከቱበት ቦታ ላይ ራሱን በላስቲክ የውሃ መያዣ በያዘው ቤንዚን አቃጠለ፡፡
በሥፍራው የነበሩ ሰዎች በውሃ እና ለፍራፍሬ ንግድ ከለላ የተደረገ ህንፃ ሲሰራ እንደ ከለላ የሚጠቀሙበት ሸራ መሰል ነገር፤ በማንሳትና በማራገፍ እሳቱን ሊያጠፉለት ቢሞክሩም ግለሰቡ ተውኝ መሞት መፈለጌን ህዝብና መንግሥት እንዲያውቅልኝ እፈልጋለሁ ብሏል ሲሉ የዐይን እማኞች ተናግረዋል፡፡
እንደ እማኞች ገለፃ ግለሰቡ ከወገቡ በላይ ሙሉ በሙሉ ተቃጥሎ ቆዳው የተኮማተረ ሲሆን ጀርባው በእሳቱ በእጅጉ የተጎዳ ሲሆን፣ ጸጉሩም መርገፍ ጀምሮ አይኑ ብቻ ከጉዳት ተርፏል፡፡
ዘጋቢያችን 11፡ 30 ሰዓት ላይ ከሥፍራው ሲደርስ ራሱን ያቃጠለው ግለሰብ የለበሰው ጃኬት እንደ ወረቀት አሮ ወዳድቆ፣ ወይን ጠጅ ነጠብጣብ ያለው የተቃጠለ ሸሚዝ ቁርጥራጭ ወዳድቆ የተመለከተ ሲሆን ግለሰቡን ፌዴራል ፖሊስ በፓትሮል መኪና መወሰዱን እማኞች ነግረውት የቀይ መስቀል አምፑላን መጥቶ ፖሊስ ወስዶታል ተብሎ ባዶውን ሲመለስ ከሥፍራው ታዝቧል፡፡
ዘጋቢያችን ከሥፍራው በእቡእ እማኞችን ለማናገር የሞከረ ሲሆን ሁኔታውን እየሰቀጠጣቸው የተመለከቱ በአካባቢው የጋዜጣ፣ የመጽሔት ንግድ ላይ የነበሩ እማኞች ሰውየው ከታክሲ መውረዱንና በወቅቱ በአኳ ላስቲክ የያዘው ቤንዚን ሳይሆን ውሃ እንደመሰላቸውና ንግግርም ሲያደርግ ትኩረት እንዳልሰጡት ገልጸዋል፡፡
ቤንዚኑን ራሱ ላይ በመላ አካላቱ እያፈሰሰ ሁለት ጊዜ ክብሪት ሲጭር እምቢ ብሎት በሦስተኛው ቦግ ብሎ መንደድ እንደጀመረና እየሮጠ ወደ አውቶብስ ተጠጋ በማለት የገለጹት እማኞች፣ የአውቶብስ ሹፌር በሮቹን ዘግቶበት ተመልሶ የማስታወቂያ መመልከቻው ቦታ ላይ ተዝለፍልፎ በመውደቁ ሰዎች እየተሯሯጡ ውሃ በማፍሰስ እና በሸራ በመጠቅለል ሊያጠፉለት ቢሞክሩም እስትንፋሱ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋም ጉዳቱ ከፍተኛ ሆኗልብለዋል፡፡
የፌዴራል ፖሊስም ወደ ሥፍራው በፍጥነት በመምጣት ሰዎችን በትኖ የሚያጣጥረውን ግለሰብ በፓትሮል መኪና በመውሰድ በአካባቢው በቅርብ የተመለከቱ ሰዎችን ሰብስቦ እዚያው አካባቢ የሚገኝ አንድ ቅጥር ጊቢ ሰብስቦ የሞባይል ስልካቸውን በመንጠቅና በማስፈራራት ጊቢውን ዘግቶ አግቷቸዋል ብለዋል፡፡
በአካባቢው የሥራ ማስታወቂያ ስትመለከት የነበረች አንዲት ግለሰብ ጎልማሳው በሰውነቱ ደህና የሚባል ሰው ሲሆን ጸአዳ ስኒከር ጫማ ግሬይ ጅንስ ሱሪና ወይን ጠጅ ሸሚዝ ከጃኬት ጋር መልበሱን በእድሜውም ከ25 እስከ 35 ሊደርስ እንደሚችል ለዘጋቢያችን ገልፃ ከታክሲ ወይም ከባስ መውረዱን ያዩት ሰዎች ነግረውኛል እኔ ግን ሲቃጠል ብቻ ነው የተመለከትኩት ስትል እንባ እየተተናነቃት ለዘጋቢያችን ገልጻለች፡፡
ዘጋቢያችን በቦታው ባደረገው ቅኝት ግለሰቡ ወደቀ የተባለበት ሥፍራው ላይ የልብሶቹ ቁርጥራጮችን፣ እሳቱን ሊያጠፉበት የሞከሩትን ሸራ መሳይ ላይለን፣ በውሃ የረጠበ ሥፍራ ተመልክቷል፤ የፌዴራል ፖሊስም ሰዎችን አግቶ እና አንድ ግለሰብን ደግሞ (እማኞች በሞባይል ለመቅረጽ ሞክሮ ነበር ብለዋል) አንበርክከው ሲመቱት ተመልክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሪፖርተርና የካሜራ ጋዜጠኛ በሥፍራው ተገኝተው ቦታውን ቀርጸው ሁኔታውን የተመለከቱ ሴት እማኞችን ቃለ መጠይቅ ያደረጉ ሲሆን የደህንነት ሰዎች መጥተው እንዳይቀርጹ ሲከለክሏቸው እኛ ኢቲቪዎች ነን ሥራችንን እንስራበት በማለት ቀረፃቸውንና ቃለ- መጠይቃቸውን የቀጠሉ ሲሆን የደህንነት ሠራተኞቹም ለዘብ ብለው ሰዎችን ወደ መበተኑና ወደ መጠጋጋቱ ሲያመሩ ዘጋቢያችን አስተውሏል፡፡

Eritreans are asking:" Is Isaias dead or alive?"

ADDIS ABABA (Reuters) – Eritrea has sought to quash speculation about President Isaias Afewerki’s health, saying he was “fit as a fiddle” and lambasting the United States for spreading “lies” over his condition.

Rumours have been rife in the past few years that Isaias, 66 and in power since 1993 after leading his country to independence from Ethiopia, was in poor health and required regular trips abroad for treatment.
Speculation about his health has stirred up debate over who might eventually replace the reclusive leader. Isaias has no obvious successor but the opposition says he might be grooming his son, Abraham, for the top job.

U.S. diplomatic cables released by WikiLeaks have also mentioned the possibility of the military elite trying to take over power in the Red Sea state.
Eritrea refuted speculation about his health late on Sunday in a special announcement aired by the information ministry on state television and later broadcast on the Internet.
“There has been widespread speculation in the past few weeks that President Isaias has fallen seriously ill,” the broadcast said.
“We would like to announce that President Isaias is fit as a fiddle and is in the best of health under all criteria,” it added in remarks translated from the Tigrinya language.
Eritrea’s exiled opposition has alleged on numerous occasions that the president is suffering from a serious liver ailment and that he has been receiving medical attention in Qatar, with which his nation has close ties.
In a move aimed at highlighting his good health, the broadcast showed a montage of Isaias sporting a baseball cap and making a short dash down a dirt track as he waved to bystanders in light rain.
It also pictured the leader snapping pictures with a point-and-shoot camera, then walking up a slope and posing as he smiled alongside other men on the banks of a reservoir.
Eritrea accused the U.S. Central Intelligence Agency (CIA) of spreading the “lies” surrounding its leader’s health.
In a leaked cable from the U.S. embassy in the capital Asmara, former U.S. ambassador Ronald McMullen said Isaias feared the U.S. would try to kill him by firing a missile on his residence in the coastal city of Massawa.
Asmara often criticises Washington which it says backs its arch rival Ethiopia in the two countries’ frontier dispute.
“Those lies emanate from Langley with the CIA being the rumour-mongers,” said the television announcement, referring to the intelligence agency’s headquarters.
Eritrea and Ethiopia have been at loggerheads since their 1998-2000 border war, which killed 70,000 people, and they accuse one another of backing the other’s rebels and working to topple the other’s government.
Isaias accused Washington last month of plotting Ethiopian cross-border raids that targeted alleged rebel camps.
(Editing by George Obulutsa and Maria Golovnina)

Monday, April 23, 2012

መንግስት ሙስሊሙ ያቀረበውን ጥያቄ በሀይል ለመፍታት ቆርጦ ተነስቷል


ኢሳት ዜና:-ከሳምንት ሳምንት እየተጠናከረ የመጣው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ፣ መላው ክርስቲያኖችንን እንዲያካትት ጥሪ እየተላለፈ ባለበት በአሁኑ ወቅት መንግስት ችግሩን በሰላም ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ የሀይል አማራጭን ለመጠቀም ፍላጎት እያሳየ ነው።
የአቶ መለስ ዜናዊን የሰሞኑን የፓርላማ ንግግር ተከትሎ በመላ አገሪቱ የሚገኙ በርካታ ሙስሊሞች ባለፈው አርብ ተቃውሞዓቸውን ካሰሙ በሁዋላ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከመንግስት ጋር በመተባባር ጥያቄውን በሀይል ለመፍታት ፍላጎት አሳይቷል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከተለያዩ የክልል ኡላማዎች፣ ከዞን እና ከወረዳ ምክር ቤት ሀላፊዎች ጋር በጋራ ተመካክሮ ባሳለፈው አቋም ፣ አክራሪነት መንፈስ የተጠናወታቸው  አካላት ህዝበ ሙስሊሙ ሀይማኖቱን ተረጋግቶ እንዳያካሂድ እያደረጉት በመሆኑ ፣ ህብረተሰቡና የጸጥታ አስከባሪዎች ግለሰቦቹን እየያዙ ለህግ ማቅረብ እንዳለባቸው ውሳኔ አሳልፎአል። 
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ አህመዲን ሼህ አብዱላሂ ባለድርሻዎች አክራሪዎችን እየመረጡ ወደ ህግ እንዲያቀርቡዋቸው ጠይቀዋል።
የኢሳት የዜና ምንጮች እንደሚገልጡት ከሆነ በእየሳምንቱ የሚታየው የሙስሊሞች እንቅስቃሴ ኢህአዴግንና ደጋፊዎችን፣ መንግስትን እና ተከታይ ኡላማዎችን በእጅጉ እያስደነገጠ ነው። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሁለት ምርጫዎች አሉት፣ አንድም ሙስሊሙ የሚያቀርበው ጥያቄ የብዙሀኑ ጥያቄ መሆኑን ተረድቶ ለጥያቄው አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀት፣ ሌላም ጥያቄው የጥቂቶች ነው በሚል በሀይል ለመጨፍለቅ መሞከር ነው።
አንደኛው አማራጭ እውን ከሆነ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ህዝብም ትልቅ ትምህርት ጥሎ ያልፋል የሚሉት ተንታኞች፣ መንግስት በህዝብ ግፊት ጥያቄዎችን መመለስ ከጀመረ ሌሎችም በተመሳሳይ መልኩ ጥያቄያቸውን እየያዙ ለመቅረብ ድፍረቱን ያገኛሉ ይላሉ። መንግስት ጥያቄውን በሰላም ለመመለስ ከፈቀደ ከሁሉም በላይ ተጠቃሚው መንግስት ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ይሆናል፣ ምክንያቱም ህዝብ በጋራ ከተነሳ መንግስትን ማስገደድ እንደሚችል ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ወይም ሊቢያ ድረስ ሳይጓዝ በራሱ አገር ጥሩ ትምህርት ይቀስማል፣ ቀዳዳውም እየሰፋ ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎችን ለማቅረብ ይደፋፈራሉ ይላሉ።
ተንታኞቹ እንደሚሉት መንግስት ጥያቄውን በሀይል ለመጨፍለቅ ከሞከረም፣ መላው ሙስሊም በጋራ እና በቁጭት እንዲነሳ እንደሚያደርገው እስካሁን የተከተለውን ፍጽም ሰላማዊ ተቃውሞ ወደ ሀይል ተቃውሞ ሊቀይረውና ደም መፋሰስ ሊከተል እንደሚችል ያስጠነቅቃሉ። ሙስሊሙ ህብረተሰብ በጀመረው ፍጹም ሰላማዊ ትግል መቀጠሉ መንግስት የሚያስደነብረው ይሆናል ሲሉም ያክላሉ።
በሌላ በኩል ግን ሙስሊሙ ያቀረበው ጥያቄ ብሄራዊ አጀንዳ እንዲኖረውና ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ካስፈለገ፣ ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ ለማጋጨት በአቶ መለስ መንግስት የተሸረበውን የመከፋፈል ሴራ ማክሸፍ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ነገር መሆኑን አንዳንድ ተንታኞች ይናገራሉ። አቶ መለስ በሰሞኑ የፓርላማ ንግግራቸው ክርስቲያኑ ህዝብ ደንብሮ ከመንግስት ጎን እንዲቆም ለማድረግ ቢሞክሩም፣ በሙስሊም ሆነ በክርስቲያኑ በኩል ያጋጠማቸው ተቃውሞ እንጅ ድጋፍ አለመሆኑን ተንታኞች ይገልጣሉ። ክርሰቲያኑ ህዝብ አቶ መለስ ገዳማትን ሳይቀር ለማውደም ሲሞክሩ እያየ ለእርሳቸው ቅስቀሳ ጆሮ አይሰጥም የሚሉት ተንታኞች፣ ይሁን እንጅ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ጥያቄያቸው በዘላቂነት ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲያገኝ ከፈለጉ ክርስቲያኑን ወገን ለማቀፍ ጥረት ማድረግ አለባቸው። የሙስሊሙ ጥያቄ በዘላቂነት ሊፈታ የሚችለው አገራዊ ችግሮች ሲፈቱ በመሆኑ፣ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ለእነዚህ አገራዊ ችግሮች ቅድሚያ በመስጠት መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ  የሚያሳትፍ መርሀ ግብር ሊነድፉ እንደሚገባ ያሰምሩበታል።
መንግስት በሚወስደው እርምጃ ግራ መጋባቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። ሰሞኑን የተወሰኑ ሙስሊሞችን ለማሰር እንቅስቃሴ ቢያደርግም አዝማሚያው ስላስፈራው መልሶ ለቋቸዋል።

የቴዲ አፍሮ አልበም ሽያጭ ሬከርድ አስመዘገበ

ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የተለቀቀው የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ‹‹ጥቁር ሰው›› አልበም በ300 ሺሕ ሲዲና በ120 ሺሕ ካሴት ሽያጭ፣ በአጠቃላይ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ አሥር ሚሊዮን ብር ገደማ በማስገባት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ ታሪክ አዲስ ሬከርድ ማስመዝገቡ ታወቀ፡፡ ሽያጩ የተመዘገበው አልበሙን ከአዲካ ኮሙዩኒኬሽንና ኢቨንትስ ተቀብለው በማከፋፈል እየሸጡ ካሉት ከኤሌክትራና ከአምባሰል ሙዚቃ ቤቶች፣ እንዲሁም ከጣና ኢንተርቴይንመንት ነው፡፡ ኤሌክትራና አምባሰል ሙዚቃ ቤቶች በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ለሽያጭ ሲያቀርቡ፣ ጣና ኢንተርቴይንመንት በሰሜን ኢትዮጵያ ያከፋፍላል፡፡ 

አዲካ ለሙዚቃ ቤቶቹ እያንዳንዱን ሲዲ በብር 17.50 እያንዳንዱን ካሴት ደግሞ በዘጠኝ ብር ሲያስረክብ፣ ገበያው ውስጥ አንዱ ሲዲ 25 ብር አንዱ ካሴት ደግሞ 13 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳ አንዱ ሲዲ በተወሰነለት ዋጋ እንዲሸጥ ቢታሰብም በየመንገዱ እስከ ሃምሳ ብር እንደተሸጠ ታውቋል፡፡ 

አዲካ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከሽያጮቹ 6.3 ሚሊዮን ብር ያገኘ ሲሆን፣ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ለሙዚቃ ቤቶቹና መንገድ ላይ ለሚሸጡ ገቢ ይሆናል፡፡ አልበሙ ከወጣበት ሚያዝያ 6 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ በብዛት እየተሸጠ መሆኑም ታውቋል፡፡ 
በተለይም አልበሙ በወጣበት ሚያዝያ 6 ቀን በርካታ ሰዎች በሙዚቃ ቤቶች ደጃፍ ወረፋ ሲጠብቁና ሌሎችም መንገድ ላይ ካሉ ሻጮች በጭማሪ ዋጋ ሲገዙ ታይተዋል፡፡ 

‹‹በተለያዩ ሚዲያዎች የሙዚቃ አፍቃሪያን ከተወሰነው ዋጋ በላይ አውጥተው አልበሙን እንዳይገዙ ብናስታውቅም፣ አንዳንድ ነጋዴዎች እጥረት ያለ አስመስለው ከተተመነው ዋጋ በላይ ሲሸጡ ነበር፤›› በማለት የአዲካ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዘለቀ ገልጸዋል፡፡ 

አቶ አሸናፊ ለሪፖርተር እንዳስረዱት፣ 500 ሺሕ ሲዲዎችና 200 ሺሕ ካሴቶች ሙዚቃ ቤቶቹ እንደሚያስፈልጋቸው በመጀመርያ ስላስታወቁ አልበሙ አሁንም እየታተመ ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ አልበሙ በአዲካ ወኪሎች በኩል በውጭ አገር በመሸጥ ላይ ቢሆንም፣ አቶ አሸናፊ ግን ምን ያህል ኮፒዎች አንደተሸጡ ገና አልታወቀም ብለዋል፡፡ 

ከአሁን ቀደም ለገበያ ከቀረቡ የሙዚቃ ሥራዎች ከፍተኛ ሽያጭ በማስመዝገብ የአገሪቱን ሬከርድ ይዟል የተባለለት የቴዲ አፍሮ አልበም መሆኑን በሙዚቃው ዘርፍ ውስጥ ያሉ ይስማማሉ፡፡ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ እንኳን 300 ሺሕ ሲዲ መሸጥ ይቅርና ኦሪጂናል አልበም ለመሸጥ ከፍተኛ ችግር እንደነበር በሙዚቃ ዘርፍ ውስጥ ያሉ ይስማሙበታል፡፡ 

በተለይም ከቅጂ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ በርካታ የሙዚቃ ሰዎች ተስፋ እስከ መቁረጥ መድረሳቸውም ይታወሳል፡፡ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ የሙዚቃ ባለሙያ፣ ‹‹የቴዲ አፍሮ አልበም ሽያጭ የአገሪቱ ሬከርድ ሲሆን፣ ምናልባት ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ኢንዱስትሪም ዓይን ከፋች ሊሆን ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ አልበሙ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ቢያገኝም እሳቸው ግን በግላቸው የተለየ አመለካከት እንዳላቸው ገልጸው፣ ዝርዝር ውስጥ ገብተው ከመናገር እንደሚቆጠቡ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ሕዝብ ሆ ብሎ የተቀበለውን ነገር ለመተቸት መነሳት ለጊዜው አስፈላጊ አይደለም፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡


ሪፖርተር እንደዘገበው

እስክንድር ነጋን ሳስበው ሳስበው …፪


በተመስገን ደሳለኝ
ሰኞ ቀንን ደባሪ ነው ይሉታል-በተለምዶ፡፡ ለጋዜጠኛ ግን ሰኞን ከእሁድ የሚለየው እኩል አለመከሰታቸው ብቻ ነው። በተረፈ በእኛ ሙያ ደባሪ ወይም አስደሳች ቀን የሚለያዩት በስማቸው (ሰኞ፣ ማክሰኞ፣ ዕረቡ…) ተብለው ሳይሆን በየቀኑ በሚከሰተው የዜና እና የመረጃ ክብደት ነው። እናማ ሚያዝያ 1 ቀን 2004 ዓ.ም የዋለው ሰኞ ለእኔ ደባሪ አልነበረም። እንዲያውም በጣም ከተደሰትኩባቸው ጥቂት ቀናቶች አንዱ ነው። ለምን መሰለህ? በጠቀስኩት ዕለት ከአሲምባ (ከመኖሪያ ቤቴ) እንደወጣሁ ለስራ ጉዳይ የቀጠርኳቸው የተለያዩ ሰዎች ስለነበሩ ፈጠን ፈጠን ብዬ ጉዳዬን ለመጨረስ መዋተት ጀመርኩ። ሰአቱም እንዲህ እንዲህ እያለ እኩል ቀን ላይ ደረሰ። እለቱ ብራም ስለነበር መንፈስን አይጨፈግግም። እንዲህ አይነት የአየር ንብረት ደግሞ ዘና ስለሚያደርግ ጥቂት የእግር ጉዞ (ወክ) ለማድረግ ይጋብዛል። እናም የጐዳናውን ጥግ ይዤ አራት ኪሎን ሰንጥቄ ወደ ፒያሳ ድንበር ተጠጋሁ፣ ይህን ጊዜም ድንገት ተንቀሳቃሽ ስልኬ የ‹‹አድምጠኝ›› ኡኡታዋን አሰማች። ለአፍታ ያህልም የተደወለውን ቁጥር አየት አድርጌ ‹‹ሀሎ›› ስል መልስ ሰጠሁ፣ ከመቅፅበትም በደስታ ሲቃ የታፈነ ድምፅ ምላሽ ሰጠኝ። የእስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሠርካለም ፋሲል ነበረች-የደወለችው፡፡ የደስታዋ ድምፅም በውስጤ ዘለለ። ቦርቅ ቦርቅ፣ ዝለል ዝለል፣ ጨረቃን ንካ ንካ… የሚል ስሜት ወረረኝ። ስልኩን ዘግቼው እንኳ ያ አብሳሪ ድምጽ ማስተጋባቱን አላቋረጠም ‹‹እስክንድርን ፔን ኢንተርናሽናል የ2012 ተሸላሚ ጋዜጠኛ አድርጎ መረጠው፡፡›› ደጋግሞ አቃጨለብኝ፡፡ እናም በጎዳናው ላይ ድምፄ እስኪሰማ ‹‹እስክንድር ጀግና ነህና ይገባሃል!!›› እያልኩ ጮኽኩ፡፡
ጥሎብኝ ጀግና እወዳለሁ። ብዙ ጀግኖች ከልቤ ቀርተዋል። ዳግማዊ ቴዎድሮስ እና ዳግማዊ ምንሊክን ከልብ እወዳቸዋለሁ። ስለ አሉላ አባነጋ እና ዘርአይ ደረሰም ባወራ ባወራ አይሰለቸኝም፡፡ በተለይ ደግሞ ብዙ ለፍቶ ተገቢውን ዋጋ ያላገኘው ዘርአይ ደረስ ከምንም በላይ ያሳዝነኛል። መቼም ዛሬ ዘርአይ በህይወት ቢኖር የሞተላት ኢትዮጵያ ቀኝ ገዢ፣ የተወለደበት ክፍለሀገር ኤርትራ ደግሞ ቀኝ ተገዥ ሆነው ስለተገኙ ተለያይተዋል መባሉን ሲሰማ ምን ሊሆን እንደሚችል ሳስበው ያስደነግጠኛል። አብዲሳ አጋ፣ ጄኔራል ፋንታ በላይ እና ጄኔራል ኃየሎም አርዕያም እንዲሁ ይመቹኛል። እነዚህ እንግዲህ የጦር ጀግና ናቸው። …እንዳልኩህ መንግስቱ ኃ/ማሪያምን እና መለስ ዜናዊን ደግሞ ለመውደድ እና ለመቀበል አስብና አንዳች የሚያስወድድ ምክንያት እያጣሁ ደክሞኝ እተወዋለሁ፡፡ አንዳች እንኳ…
አሜሪካኖቹ እንደሚሉት ሲቪል ጀግኖችም አሉ። ከእነዚህ ሲቪል ጀግኖች ለዘላለም የወደድኩት አንድ ሰው አለ-አበበ ቢቂላ የሚባል። ኦ አቤ የእኔ ጀግና። መቼም አበበ ቢቂላን የማያውቀው የለም። ሌላው ቀርቶ በወቅቱ ‹‹የአፍሪካ አባት›› ተብለው ከተሰየሙት አፄ ኃይለስላሴ የማይተናነስ ስምና ዝና ነበረው። ኧረ እንዲያውም የማታ ማታ የውጭ ሀገር ሰዎች ኢትዮጵያን ያስታውሱበት የነበረው ‹‹የኃይለስላሴ ሀገር›› የምትለው ቅጥያ ‹‹የአበበ ቢቂላ ሀገር›› በሚል እስከመቀየር ደርሶ ነበር። ይህ ብርቱ ሰው በሮም ኦሎምፒክ ማራቶን፣ ያውም በባዶ እገሩ ሮጦ አሸንፎአል። ከአፍሪካ የመጀመሪያው የወርቅ ተሸላሚ ሲሆን ከአለምም 42 ኪሎ ሜትርን በባዶ እግር ሮጦ ያሸነፈ የመጀመሪያው ሰው ነው። አቤ በዛ ኦሎምፒክ ያሸነፈው ማራቶንን ብቻ አይደለም። የጣሊያንን ወራሪን የቅኝ ገዥ መንፈስም ነው። የውድድሩ ዕርቀት የሮም አደባባይን መዞርን ያካትት ነበር። በሮም አደባባይ ደግሞ ከኢትዮጵያ የተወሰደው የአክሱም ሀውልት (በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል) ተገትሮአል። ምንም እንኳ ሀውልቱ የጣሊያንን ዘራፊነት መስካሪ ቢሆንም፣ ጣሊያኖች ግን የአሸናፊነታቸው ወይም የአድዋን ሽንፈት በቀል ለመወጣታቸው መገለጫ አድርገው ያዩት ነበር። እናም አቤ ሀውልቱ ጋር ሲደርስ በጣም ፍጥነት ጨመረ። ይህን የታዘበው ጋዜጠኛም ውድድሩ ከአለቀ በኋላ አቤን ጠየቀው ‹‹ሀውልቱ ጋ ስትደርስ ምን ተሰማህ?›› አቤም መለሰ ‹‹ደም ፍላቴ መጣ!›› እነሆ ይህ ከሆነ ከብዙ አመት በኋላ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ‹‹‹የአክሱም ሀውልት ለወላይታው ምኑ ነው?›› አሉና አረፉት። በዚህ አባባላቸውም እነ አቤ ሀውልቱ እንደማይመለከታቸው አረዱን። እርግጥ ይህ ፖለቲካ ነው። ሆኖም ጥሩ ያልሆነ ፖለቲካ ስለመሆኑ ግን አንዳች ጥርጣሬ አይግባህ።
የሆነ ሆኖ አቤ በሮም የጀመረውን ድል በቶኪዮም ደግሞታል። ይህ ብቻ አይደለም የአካል ጉዳት ከደረሰበት በኋላም በዊልቸር ተወዳድሮ አሸንፎአል። አይበገሬነት ይሉሃልም ይሄ ነው፤ ሌላ አይደለም። እስክንድር ነጋ ማለትም ይህ ነው፣ ሌላ አይደለም። ታስሮም እንኳ አለም ያከበረው፡፡
መቼም ስለዚህ ብርቱ ሰው መፃፍ በራሱ ደስታን ይፈጥራል። ዛሬ እስር ቤት ከገባ ስምንተኛ ወሩን ይዞአል፤ በታሰረ በ10ኛው ቀን በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ ‹‹እስክንድር ነጋን ሳስበው፣ ሳስበው…›› በሚል ርዕስ ስለወጣው ዳገት፣ ስለከፈለው ዋጋ፣ በምርጫ 97 ማግስት ከነፍሰጡር ባለቤቱ ጋር በቃሊቲ እስር ቤት መግባቱን፣ ባለቤቱም በዛው እስር ቤት የመጀመሪያቸውን ወንድ ልጅ እንደተገላገለች… ፅፌልህ እንደነበር ታስታውሳለህ፡፡ እነሆ ዛሬ ደግሞ ክፍል ሁለትን ልፅፍልህ የተነሳሁት የአለም አቀፍ ተሸላሚ መሆኑን ተከትዬ ነው። ዜናው በይፋ የተገለፀው የዛሬ ሳምንት ነው።
እንዳልኩህ እስክንድር ነጋ ተራ ጋዜጠኛ ወይም ተራ ተንታኝ አይደለም። ለእኔ ከእነ አሉላ አባነጋ፣ ከእነ ዘርዕይ ደረስ፣ ከእነ አብዲሳ አጋ ትይዩ የሚቆም የሀገር ባለውለታ ነው። ሲቪል ጀግና ነው፡፡ ‹‹የያዝኩትን መሬት እንዳልቅ›› የመንፈስ ብርታት የሆነኝም ይህ ሰው ነው። በዚህ ሰው ዘመን ተገኝተህ፣ በዚህ ሰው ሙያ መሰማራት ደግሞ ምን ያህል ልብ እንደሚያሞቅ ልነገርህ አልችልም። ልክ ፕሌቶ የተባለው ግሪካዊ ፈላስፋ ‹‹ከምንም በላይ ሶቅራጥስ በነበረበት ዘመን እንድኖር ስላደረከኝ አመሰግናሃለሁ›› እንዳለው አይነት ምስገናም በልቤ አቀረብኩ፡፡
በእርግጥ እስክንድር ዛሬ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ነው። ወደቃሊቲ ከመላኩ በፊት ማዕከላዊ ነበረ። ማዕከላዊ የታሰሩ እስረኞች በወዳጅ ዘመድ እንዲጠየቁ ተፈቅዶላቸው ሳለም እሱ አልተፈቀደለትምና ‹‹አይዞህ›› ለማለት እንኳ አልቻልኩም። እናም ለወራት አላየሁትም። ከታሰረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜም ያገኘሁት ቃሊቲ ከሄደ በኋላ ነው። ነገር ግን በቃሊቲ ሳገኘው በአካል ከእስሩ በፊት የማውቀውን እስክንድርን አልነበረም፡፡ የመንፈስ ጥንካሬው ያልተለየውና የሞራል ልዕልናው እንዳለ ቢሆንም አካሉ ተጎሳቁሏል። ፊቱ ጠልሽቷል። ሰውነቱ በእጅጉ ከስቷል፡፡ እመነኝ ገፅታውን ገና እንዳየከው የማታውቀው ሀዘን ከልብህ ይሰነቀራል። አንዳች ያህል ምሬትም አፍህን ይሞላዋል። በዚህ ላይ ገና ‹‹ክፉና ደግ›› ያለየ የአምስት አመት ልጁ አብሮኝ ስለነበረ የአባትና የልጅ ናፍቆት እና ፍቅር ልውውጥን ለመመልከት በእጅጉ ጠንካራ መሆንን ይጠይቃል። እምባ እንዳይፈስ መታገልንም ይፈልጋል። ስሜትህ ይደፈርሳል። ያጥወለውልሀል። በተለይ የአባትየው የበኹር ልጁን አንገቱ ስር ወሽቆ ግብግብ ሲል ማየት ብቻ ለዘላለም ከአይነ ህሊና የማይጠፋ የስቃይ ስሜት ይፈጥርብሃል።
የሆነ ሆኖ ናፍቆትን ከአንገቱ ስር እንደሸጎጠው ጥቂት ቃላቶችን ተለዋወጥን።
‹‹ምን ሆነህ ነው ሰውነትህ የተጎሳቆለው?››
‹‹ማዕከላዊ እያለሁ አሞኝ ነበር››
‹‹ታዲያ አሁን እንዴት ነህ?››
‹‹በጣም ሰላም ነኝ፣ ተሽሎኛል። ፍትህ እንዴት ነች? ማዕከላዊ እያለሁ አገኛት ነበር። እዚህ ግን ስለማይፈቀድ አላገኛትም››
‹‹ደህና ነች። ስለክሱ ምን እያሰብክ ነው?››
‹‹ክሱ ምንም ይሁን ምን አያሳስበኝም። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ እስክንድር ነጋ አሸባሪ እንዳልሆነ ያውቃል። አንተም ታውቀኛለህ››
‹‹አውቅሃለሁ። ለሀገርህ ከላይ ታች ስትል ህይወትህን በቅጡ እንዳልኖርክም አውቃለሁ። ብቻ አይዞህ በርታ››
‹‹ለእኔ አታስብ አንተ በርታ። ስራህን በጥንካሬ ስራ››
ይህንን ጊዜ ጭውውታችንን ጠጋ ብሎ ያደምጥ የነበረው የማረሚያ ቤቱ ፖሊስ ‹‹በቃ! ሰዓት ደርሶአል›› ሲል በትህትና አቋረጠን፡፡ ሆኖም በዚህ መሀል በፍጥነት ስለክሱ፣ እንዲሁም ድንገት ፍርድ ቤቱ ተከላከል ቢባል እንኳ እውነቱን የኢትዮጵያ ህዝብ ያውቀው ዘንድ እንዴት መከላከል እንዳለበት ስለመከላከያ ምስክሮቹ አውርተን ተለያየን።
ምሬት በልቤ እንደገባ የወህኒ ቤቱን ግቢ ለቀኩ። …ብዙ ነገርም አሰብኩ፣ ብዙ ነገር… ግና ምን ማድረግ ይቻላል? ለራሴ የጠየኩት ጥያቄ ነው። እኛስ ብንሆን እስከመቼ ነው ‹‹እከሌ ታሰረ፣ እከሌ በይቅርታ ተፈታ፣ እከሊት ተፈረደባት… እያልን ዜና ስንሰራ የምንውለው? በዚህ አጀንዳስ ሰለምንድን ነው ‹ቢዚ› እንድንሆን የተደረግነው? እኮ ሀገሩን የሚወድ፣ ለሀገሩ ራዕይ ያለው እየታሰረ፣ ራዕይ የሌለው እያሰረ እስከመቼ…›› ያጨናነቁኝ ጥያቄዎች ቢሆኑም ምላሽ እንደሌላቸው አውቃለሁ። እለቱ ደባሪ ሆነብኝ። የእስክንድር ገፅታ፣ ከልጁ ናፍቆት ጋር ናፍቆቱን ለመወጣት ያደርግ የነበረው ነገር በሙሉ ደጋግሞ እየመጣብኝ ቀኔን ብልሽትሽት አደረገው። ደግነቱ የቱንም ያህል ብከፋ፣ የቱንም ያህል ባዝን፣ የቱንም ያህል… ተስፋ የመቁረጥ ስሜት አይመጣብኝም። ይህማ እንዴት ይሆናል? ጉዳዩ የሀገር ጉዳይስ አይደል እንዴ? ያውም የምንወዳት ኢትዮጵያ፡፡ (መቼም ኢትዮጵያውን ለኢትዮጵያ መሞታቸው እንደሁ ዛሬም አላቋረጠም፡፡ ዘላለማቸውን ለትግል የተፈጠሩ ያልተሳካላቸው ታጋዮች… ዳሩ የሀገር አንድነት ሲናጋ እና አንዱ ብሄር በሌላው ላይ እንዲነሳ የሚጋብዝ ፖለቲካ በስራ ላይ ሲውል ካልሞትን መቼ ልንሞት ነው? አዎ! አሊያማ ‹‹ኢትዮጵያ የእኛ መመኪያ…›› ዘፈን ብቻ ሆኖ ሊቀር ነው?)
የሆነ ሆኖ በቀጣዩ ሳምንትም ይህን ጀግና ለመጠየቅ አስቤ ለባለቤቱ አብረን እንሄድ ዘንድ ደወልኩላት። ሆኖም የመለሰችልኝ መልስ ምድርና ሰማዩን አዞረብኝ። ነገር አለሙ ድብልቅልቅ አለብኝ። የጋዜጠኛ ሠርካለም አጭር መልስ እንዲህ የሚል ነበር፡-
‹‹ውይ! ተሜ ባለፈው ጠይቀከው ከሄድክ በኋላ ከእኔ፣ ከልጁ እና ከአንዲት ዘመዳችን በስተቀር ማንም ሰው እንዳይጠይቀው ተደርጓል!››
አሁን ጩኽ፣ ጩኽ… አለኝ። ግና ምን ብዬ ልጩኽ? ወደማንስ ነው የምጮኸው? አምስት ልጆች የወለደችለትን የሰማኒያ ሚስቱን በመጥረቢያ ጨፍጭፎ የገደለ ወይም በጠራራ ፀሐይ ማጅራት ሲመታ የተያዘ… ያለገደብ በወዳጅ ዘመድ ሲጠየቅ፤ ከእነ አብዲሳ አጋ እና ዘርዐይ ደረስ ተርታ የሚሰለፈው የሀገር ባለውለታ እስክንድር ነጋ በሶስት ሰው ብቻ፤ እሱም በውስን ሰዓት (ከሰኞ እስከ አርብ ለ10 ደቂቃ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ለ30 ደቂቃ) እዚህ ሀገር ምንድር ነው እየተደረገ ያለው? በዚህ ሁኔታ እስከ መቼ ነው የምንዘልቀው? 40 ወይስ 50 አመት? በሀገሪቱ ህገ-መንግስት መሰረት እንኳ ‹‹መታሰር›› የማይቻልበት ሁኔታስ ወዴት ያደርሰናል? አስረው ሲያበቁ ጠያቂ መገደብ፣ ሲያሻው በእስረኛ ማስደብደብ.. ታዲያ የትኛው ነው ህጋዊ? ታሳሪው ወይስ አሳሪው? መልሱልኛ?
ደግሞ እኮ ጉዳዩን የከፋ የሚያደርገው ይህ አይነቱ አሰራር ነባር መሆኑ ነው። ማንም ይሁን ማን፣ የቱንም ያህል ለሀገር የለፋ ይሁን የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ተቃዋሚ ከሆነ እንኳንም ቆሞ ሞቶም አድሎ እና በደል አይቀርለትም። ለዚህም ማጠናከሪያ የሚሆን አንድ ምሳሌ እንይ።
ደህና! በእድሜዬ በሀገር ባለውለታዎች ስርዓተ ቀብር ላይ የተገኘሁት ለሁለት ሰው ብቻ ነው። ለፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ እና ለእጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሚትር አርቲስት አፍወርቅ ተክሌ (በእርግጥ በስራ ምክንያት ሳይመቸኝ ቀርቶ ቀብራቸው ላይ መገኘት ያልቻልኩባቸው አንድ ሶስት የሀገር ባለውለታዎች ነበሩ፤ ባለመቅበሬ ዛሬም ድረስ ይቆጨኛል)
ሆኖም የእነዚህ ሁለት ሰዎች የቀብር ስነ ስርዓት ጉራሜይሌ ነው። እንዴት አይነት ጉራማይሌ ይሆን? ለምሳሌ ፕሮፌሰር አስራት ወ/የስ አርበኛ ናቸው። አርበኛ ብቻም እንዳይመስሉህ ይልቁንም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በፕሬዝዳንትነት የመሩ፣ ለ40 ዓመት ከአፍሪካ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሀኪም ሆነው ሳለ ከሀገራቸው ኢትዮጵያ ሳይወጡ ያገለገሉ ናቸው። ነገር ግን የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ተቃዋሚ በመሆናቸው እና ኤርትራን አታስገንጥሉ፣ አንዱን ብሔር በሌላው ላይ አነሳስታችሁ አታጨራርሱ… በማለታቸው እስር ቤት ገቡ። በእስር ቤትም በጠና ታመው ሳለ በቂ ህክምና ሳያገኙ ቀርተው ነፍሳቸው ከስጋቸው ልትለይ ሰዓታት ሲቀር ለህክምና እንዲወጡ ፈቅደናል የሚል ቧልትን ተከትሎ እንዲወጡ ተደረገ፤ ህይወታቸውም በዛው አለፈ። ስርዓት ቀብራቸው ግን እንደብዙዎቻችን እንዲካሄድ ተወሰነ፡፡ ሌላው ቀርቶ የአርበኞች መቀበሪያ በሆነው የቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንኳ እንዲቀበሩ አልተፈቀደላቸውም። እናም በባለወልድ ቤተክርስቲያን ተቀበሩ። ወዳጄ! ኢህአዴግ ከጠላህ እንዲህ ነው፤ ሬሳህንም ቢሆን አይለቀውም፡፡
አሁን ደግሞ እጅግ ወደ ተከበሩ ሎሬት ሚትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የቀብር ስነስርዓት እንመለስ። መንግስት በይፋ ኮሚቴ አዋቅሮ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ጀምሮ ሁሉም ሚኒስትሮች የአበባ ጉንጉን ልከው፣ ስርዓተ ቀብሩ በቀጥታ የቴሌቪዥን ሽፋን አግኝቶ በስላሴ ካቴድራል የቀብር ስነስርዓታቸው ተፈፅሟል። ይህ ሁሉ ስርዓትም ሆነ የመንግስት ተሳትፎ ለአርቲስቱ ቢያንሳቸው እንጂ የሚበዛባቸው አይደለም። ምክንያቱም አፈወርቅ ኢትዮጵያን ያስጠሩ ታላቅ ባለውለተኛ ናቸውና የቀብር ስርዓታቸው ከዚህ በተሻለ ሁኔታም ቢደምቅ የሚከፋ አይኖርም፡፡
ጥያቄው ግን ሌላ ነው። ለምሳሌ አፈወርቅ አንድም ቀን ፖለቲካ ውስጥ (በተቃውሞም በድጋፍም) ገብተው አያውቁም። እናም በኢህአዴግ ‹‹ጥቁር መዝገብ›› ውስጥ ስማቸው የለም፡፡ ችግር ይኖር የነበረው በዚህ መዝገብ ቢሰፍሩ ነበር፡፡ አዎን! አፈወርቅ ተክሌ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ተቃዋሚ ቢሆኑ ኖሮስ? ብለን ካሰብን እመነኝ ቀብራቸው እንዲህ ሊሆን ቀርቶ ከፕሮፌሰሩም ያነሰ ይሆን ነበር። አየህ! ይህ ነው የሚደብረው። ይህ ነው መንግስትና ፓርቲ የተደበላለቀበት ፖለቲካ ማለት፡፡ ምክንያቱም አፈወርቅ የኢህአዴግ ተቃዋሚ ቢሆኑ እንኳ ይህ ሁሉ የሀገር ባለውለታነታቸውም ሆነ የአለም ምርጥ ሰውነታቸው ሊቀንስ ወይም ሊሰረዝ አይችልም። ፖለቲካ ሌላ ነው። ሀገር ደግሞ ከዛ የሰፋ ትልቅ ነገር ነው። ሚዛኑ እንደ መንግስት እንጂ እንደ ፓርቲ ሊታይ አይገባውም። አስራት ወልደየስ የቱንም ያህል የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ተቃዋሚ ቢሆኑም አርበኝነታቸው፣ ዩኒቨርስቲውን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው እና ለ40 አመታት ሀገራቸውን ከማገልገላቸው ጋር አንዳች የሚያያዘው ነገር የለም። ከተያየዘ ግን መጥፎ ነው፡፡ መጥፎ ፖለቲካም ይሉሃል ይህ ነው። የመንግስትን እና የፓርቲን ሚና መደበላለቅ። በእርግጥ የዚህ አይነቱ ፖለቲካ ሰለባ አስራት ወልደየስ ብቻ አይደሉም፡፡ ባለቅኔው ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህንም ናቸው፡፡ ልክ እኮ ነኝ! የእኒህ አንጋፋ የጥበብ ሰው ሞት ለኢህአዴግ ከዊትኒ ሆስተን ሳይቀር ያነሰ ነበር፡፡ ምክንያቱም የዊትኒ ሞት በመንግስት ሚዲያ የተጋነነ ሽፋን ሲያገኝ የሎሬትን ግን ያነሳውም የለ፤ ለምን መሰለህ ዊትኒ ከላይ በነገርኩህ መዝገብ ውስጥ ስሟ የለም፡፡ ፀጋዬ ገብረመድን ግን ሀገሬን አትከፋፍሉ፣ ኢትዮጵያዬን አትግደሉ፣ ታሪካችንን አታበላሹ… ያሉት ነገር በዛ በጥላቻ መዝገብ እንዲሰፍሩ አድርጎአቸዋልና ነው፡፡
የእስክንድርም ጉዳይ እንዲሁ ነው። እስክንድር በምንም ወንጀል ተጠርጥሮ ይታሰር፤ ነገር ግን ህገ መንግስቱ ከሰጠው የታሳሪዎች መብት አንዳች ሊሸረፍበት አይገባም። የመሽረፍም ስልጣን ያለው የለም፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ ህግ-መንግስቱ ጉራማይሌ ነው፡፡ ምክንያቱም ኢህአዴግ በተግባር ሲሸርፈው ‹‹ህጋዊ ነው›› ወይም ‹‹ሽብርተኝነትን ለመከላከል ነው›› የሚሉት ፈሊጥ በሰበብነት ይቀርባል፡፡ በግልባጩ ደግሞ ተቃዋሚዎች በሀሳብ ‹‹ሲሸርፉት›› ወይም ‹‹ይህ አንቀፅ ኢትዮጵያን ይከፋፍላልና ለህዝበ ውሳኔ ይቅረብ›› ሲሉ ሽብርተኝነት ነው ይልሀልና የኢህአዴግ የጫወታ ህግ ፡፡
ሌላ ጉራማይሌ
ደህና! ሌላ ጉራማይሌ እንይ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ‹‹እስክንድር ነጋ አሸባሪ ነው›› ሲል አስሮታል። በሌላ በኩል ደግሞ አለም አቀፍ ‹‹የፀሀፊዎች ነፃነት›› ተቆርቋሪ የሆነው “Pen International” ሚያዚያ 5 ቀን 2004 ዓ.ም. “Journalist Eskinder Nega wins 2012 PEN Freedom Award” በሚል ርዕስ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ እስክንድር ነጋን ‹‹a leading advocate for press freedom and freedom of expression in Ethiopia (በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት እና ሀሳብን በነፃ የመግለፅ መብት እንዲከበር በመሪነት የተጋ)›› ሲል አሞካሽቶታል። ፔተር ጎድዊን የተባሉ በአሜሪካ የፔን ኢንተርናሽናል ማዕከል ሊቀመንበርም እስክንድርን የገለፁት እንዲህ ሲሉ ነው፡-
“The Ethiopian writer Eskinder Nega is that bravest and most admirable of writers, one who picked up his pen to write things that he knew would surely put him at grave risk.”
(ኢትዮጵያዊው ፀሐፊ እስክንድር ነጋ ደፋርና በእጅጉ የሚደነቅ ፀሐፊ ነው። ብዕሩን ሲያነሳ የሚፅፍባቸው ነገሮች በእርግጠኝነት አደገኛ አደጋ ሊያመጡበት እንደሚችሉ ሁሉ ያውቃል)
የ“Freedom to write program” ዳይሬክተር ላሪ ሳይመሰ ለእስክንድር ያላቸውን አድናቆት የገለፁት “He is truly an extraordinary individual (እጅግ ልዩ ሰው)” ሲሉ ነበር።
የፔን ኢንተርናሽናል መግለጫ እንደሚያትተው እስከዛሬ ድረስ 46 ሰዎች የዚህ ሽልማት ተሸላሚ ሲሆኑ፣ 37ቱ በእስር ላይ ሳሉ የተሸለሙ ቢሆንም፣ ከእነዚህ እስረኛ ተሸላሚዎች መሀከል 33ቱ እንደተሸለሙ ወዲያውኑ ከእስር ተለቀዋል። እናስ! እስክንድር ይህን ቁጥር በአንድ ይጨምረው ይሆን?
እንግዲህ እስሩን ጉራማይሌ የሚያደርገው፣ ፖለቲካውን ደግሞ አደገኛ ቅርቃር ውስጥ የሚከተው ይህ ነው። እናም መልስ የሚያስፈልገው ጥያቄ ከዚህ ቅርቃር የምንወጣው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ዘንድ የተጉትን በማሰር እና በማሳደድ ወይስ በአሸባሪነት ከሶ ወህኒ በመወርወር? የሚለው ነው። እርግጥ ነው የዚህን ጥያቄ መልስ የሚያውቁት የስርዓቱ መሪዎች ብቻ ናቸው።